በመካከላቹ አድር ዘንድ መቅደስ ይስሩልኝ (ዘጸአት 25÷8)
ታላቅ የበረከት ጥሪ
++++ በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን +++++
ልዑል እግዚአብሔር ድንቅ ነገርን አደረገልን እርሱን የምናመልክበት በስሙ ተሰብስበን የምናወድስበት የምንቀደስበት ለኛ ሰጠን።
በአውሮፓ በሀገረ እንግሊዝ በሀደርስፊልድ ከተማ የእናታችን የቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆቿ ቅን ልቦና ተገዛ ይህ ቦታ ታላቅ ገዳም መሆን የሚችል ከዓለም ጫጫታ ወጣ ያለ ለሱባኤና ራስን ከፈጣሪ ጋር ለማገናኘት የሚችል ሲሆን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ. ካሉ ገዳማት አንዱን የሚመስል ሲሆን ነገር ግን ቤተክርስቲያኑ ቀደም ባሉት አመታት ውስጥ የሸጡልን አካላት ሲጠቀሙበት የነበረው ውስጡ ሙሉ በሙሉ ፈርሶ የተረከብን ሲሆን በቀጥታ ለእኛ ስርአት አምልኮ ለመፈፀም አመቼ ስላልሆነ በእራሳችን ዲዛይን የውስጡን ገጽታ በመከፋፈል መቅደስ፣ ቅድስት ፣ቅኔ ማህሌት እንዲሁም የተለያዩ መንፈሳዊ ስርዓት የሚፈፀምበት የኦርቶዶክስ ቀኖና በሚፈቅደው የውስጡን ስራ መስራት ጀምረናል አሁን ባለንበት ደረጃ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ቤተክርስቲያኑን ሲገዛ ከምንም አይነት እዳ ነፃ የሆነ እና ምንም እዳየሌለበት ሲሆን ካላይ የተጠቀሱትን የውስጥ ስራ እንዲሁም የቤተክርስቲያኑ በውጭ በኩል የሚሰሩ በርካታ ስራዎች ስላሉት ይህን ለመስራት የአጥቢያው ምዕመናን ለዚህ እድሳት የሚውል በመሀዲስ የዋጋ ጥናት አስጠንቶ ስራውን ለመጀመር የደብሩ ሰበካ ጉባኤ የገንዘብ እጥረት ስላጋጣመው እናት ቅን ልቦና ያላቹ የእናታችን የቅድስት ኪዳነምህርት ልጆች ዘመኑ በሚፈቅደው ቴክኖሎጂ በጎፈንድሚ ገቢ ማሰባሰብ አስፈላጊ ስለሆነ በሙሉ እምነት እንደማታሳፍሩን በማመን መተናል ።
በፀሎት፣በእውቀት፣በሀሳብ በገንዘብ ማቴሪያል በማቅረብ እንድትረዱን ስን በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን ።
ወደተራራው ውጡ ዕንጨትም አምጡ ቤቱንም ሥሩ እኔም በርሱ ደስ ይለኛል እኔም አመሰግናለሁ ይላል እግዚአብሔር ። ትንቢተ ሐጌ 1÷8
እግዚአብሔር አምላክ ቤተክርስቲያንችንን ይጠብቅ ።
የሀደርስፊልድመንፈሳዊ ሰበካ ጉባኤ አስተዳደር ጽ/ቤት
Organizer
Huddersfield Kidist Kidane Mihret Ethiopian Orthodox Church
Beneficiary

