Main fundraiser photo

Hayemanot Abebe Mekonne (ሃይማኖት አበበ መኮንን)

Donation protected
ለወገን ደራሽ ወገን ነው
   ወ/ት ሃይማኖት መኮንን ትባላለች በዴንቨርና በላስ ቬጋስ ከተማ ለብዙ ዓመታት ስትኖር ቆይታለች። በደ/ም/ቅ/ሚ/ካ ቤ/ክ ዘማሪና አገልጋይ ነበረች። ይህች እህታችን ሰው ሳትለይና ሳትመርጥ ለተቸገሩ ሰዎች ሁሉ ቀድማ ደራሽ እና የጎደለ ጓዳችንን የምትሞላ እህታችን ነበረች። ይህች እህታችን ወደ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ለመጠየቅ በሄደችበት ወቅት ባጋጠማት ሕመም ምክን ያት ለ4ዓመታት የአልጋ ቁራኛ ሆናለች። እግዚአብሔር ስለረዳን ከበፊት ጀምሮ በነበረችበት አስቸጋሪ ቦታ በማስታመምና ወጪዎችንም በመሸፈን ጥቂት ወዳጆቿ ባደረግነው ከፍተኛ ጥረት ወደ ጎንደር በማስመጣት በሆስፒታል ተኝታ እንድትታከም በማድረግ ላይ ነን። አሁን ግን ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ቀጥሎም ወደ ላስ ቬጋስ እንድትመጣ፣ የተሻለ ሕክምና እንድታገኝና ወደ ቀደመ መልካም ሕይወቷ እንድትመለስ የሁላችንንም የእርዳታ እጆች ትጠብቃለች ።
   ስለዚህ በአቶ ዳንኤል ቸኮል አማካኝነት በከፈትነው የጎፈንድሚ የገንዘብ ማሰባሰቢያ በኩል የየአቅማችሁን በመለገስ ለሰዎች ሁሉ ደራሽና አጉራሽ የሆነች እህታችንን ሕይወት እንታደግ ዘንድ በእግዚአብሔር ስም የእርዳታ እጆቻችሁን     ትዘርጉላት ዘንድ ይህንንም መልዕክት ታስተላልፉልን ዘንድ በትሕትና እንጠይቃለን። የማቴ.ወ. 25፥ 35-45
  ማሳሰቢያ፦ እርዳታዎን በሚለግሱበት ጊዜ የጎፈንድሚ ገፅ የሚጠይቅዎት ተጨማሪ ችሮታ (TIP) ወደ ተጎጂዋ እህታችን መዋጮ ውስጥ ስለማይገባ  (TIP)  የሚለው ላይ (OTHER ) የሚለውን ከመረጡ በኋላ በቲፑ ሳጥን ውስጥ ዜሮ (00) ይምሉ። በመቀጠልም የሚረዱትን የገንዘብ መጠን በዕርዳታ መስጫ ሳጥን ውስጥ ብቻ ይምሉ።
                ለተጨማሪ መረጃ አቶ ዳንኤል ቸኮል [phone redacted] ይደውሉ
                                                           እናመሰግናለን።
Donate

Donations 

    Donate

    Organizer

    Daniel Chekol
    Organizer
    Las Vegas, NV

    Your easy, powerful, and trusted home for help

    • Easy

      Donate quickly and easily

    • Powerful

      Send help right to the people and causes you care about

    • Trusted

      Your donation is protected by the GoFundMe Giving Guarantee