
የሲያትል ደብረ ምሕረት ቅ. ሚካኤል ህንጻ ቤተ ክርስቲያን መግዣ
በቅድሚያ በልዑል እግዚአብሔር ስም የከበረ ሰላምታችንን እያቀረብን በሲያትል የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ምእመናንን በአምልኮ እግዚአብሔር ልጆችን ደግሞ በምግባርና በሃይማኖት ታንጸው እንዲያድጉ በማድረግ ሰፊ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን በተጨማሪም በኀዘንም ሆነ በደስታ ጊዜ ለማህበረሰባችን የመሰባሰቢያ ማዕከል በመሆን እያገለገለ ይገኛል።
በዚህ ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን ይህንንና የመሳሰሉትን አገልግሎቶች አጠናክሮ ለማስቀጠል ያስችለን ዘንድ ካለንበት የኪራይ ቤት ወጥተን የራሳችን የሆነ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ለመግዛት ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ ላይ እንገኛለን። ለዚህም አላማ የእርስዎ ድጋፍ ስለሚያስፈልገን የበኩልዎን ድጋፍ እንዲያደርጉልን ስንል በልዑል እግዚአብሔር ስም ጥያቄያችንን እናቀርባለን፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
የሲያትል ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት
Want to join me in making a difference? I'm raising money to benefit Debre Mihret Kidus Mikael EOTC in Seattle, and any donation will help make an impact. Thanks in advance for your contribution to this cause that means so much to me.