ለአንድ ኦርቶዶክሳዊ ዋልድባ ዕምነቱ ፣ ቅርሱ ፣ ታሪኩ ነዉ ። ኦርቶዶክሳዊ ነኝ የሚል ሁሉ የዋልድባን ጉዳይ በቸልታ አይመለከተዉም::
በዋልድባ ላይ የመጣብንን የተፈጥሮ አደጋ ተቆጥጥረን አባቶቻችንን ከገዳሙ እንዳይሰደዱ ማትረፍ ሀይማኖታዊ ሀላፈነታችን ነዉ ።
ኑ በገዳሙ እስከምጽአት በሚቀመጠዉ መዝገብ ላይ የክርስትና ስማችን እናስፍር ። ዋልድባ በረከቴ ነዉ ፣ በዋልድባ አይጨከንም ፣ ስለዋልድባ ሁለቴ አላስብም ….
መራሩ ስር እንደማር እየጣፈጣቸዉ ስለ ስሜ የሚሰበሰቡበት የተቀደሰ ስፍራ ይሆናል የተባለለት ዋልድባ በጌታችን በመድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተመሰረቱ ሰባቱ መቅደሶች አንዱ የስዉራን ፣ የግኡዛን ፣ የመነኮሳት መጠለያ ገዳም ጭብጥ ቋርፍ ቀምሰዉ የበረሀ ንዳድ ሳይበግራቸዉ እንቅልፍ በማያዉቀዉ አይናቸዉ ረፍት በሌለዉ ጎናቸዉ ጠብቀዉ ያቆዪልንን አደራ ተንከባክበን ለትዉልድ እናሻግር::
በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት የዳግማዊ ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሐይማኖት ቤተክርስቲያን ይህንን የገቢ ማሰባሰቢያ አካዉንት በመክፈት ለዋልድባ ገዳም ተባባሪ በመሆን ሀይማኖታዊ ሀላፊነታችንን እንወጣ ዘንድ እና ለችግሩ የመፍትሄ አካል እንድንሆን በእግዚአብሔር ስም በማክበር እንጠይቃለን ።

