Main fundraiser photo

To secure funds for the purchase of a Church bldg

Tax deductible

                                                                     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን



የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች

ቸርነቱ ፣ ምሕረቱ ፣ ርኅራኄው የበዛ ቅዱስ እግዚአብሔር እንደበደላችን ሳይሆን እንደ ቸርነቱ ጠብቆ ለዛሬዋ ዕለት አድርሶናል።

ዛሬ ልዩ ቀን ነው። መድኃኒታችን ቅዱስ አማኑኤል እኛን በሞቀ ቤት ውስጥ እንድንኖር አድርጎ እሱ በኪራይ ቤት የሚንከራተትበት ዘመን ሊያበቃ ነው!

                                                                                            እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን!


የሚታየው እና የማይታየው መላው ዓለም በእርሱ የተፈጠረ ፣ ሁሉም የእርሱ የሆነው ጌታ አማኑኤል ፤ በግርግም ተወልዶ፣ በስደት ከቅድስት እናቱ እመቤታችን ጋር የተንከራተተ ፣ በመስቀል ተሰቅሎ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ቤዛ አድርጎ የሰጠን እና በሞቱ ሞታችንን ለውጦ በትንሳኤው ትንሳኤያችንን ያበሰረልን ኃያል አምላክ እንደ ቅዱስ ፈቃዱ ይኸው እኛ ልጆቹ ለታቦቱ ማረፊያ፣ ለክብሩ መገለጫ እንዲሆን ቤቱን ገዝተን አምላካችንን የምናመሰግንበት እኛም ከበረከቱ ተካፋይ የምንሆንበትን እድል ሰጥቶናል።

ለዚህ እድል መጠራት ታላቅ በረከት ነው!

"ቤቴንም ሥሩ፤ እኔም በእርሱ ደስ ይለኛል፥ እኔም እመሰገናለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።" ሐጌ ፩፡ ፰

እግዚአብሔር በፈቀደበት ወቅት ህንፃ ቤተ ክርስቲያን እንድንገዛ እድሉን አግኝተናል። ከባንክ ለግዢ የምንወስደውን ብድር እና የምንከፍለውን ቅድሚያ ክፍያም እያመቻቸን ነው። ከባንኩ ለምንበደረው ገንዘብ እንደ ቅድመ ሁኔታ ሊኖረን የሚገባው ከወጪ ቀሪ የገንዘብ ተቀማጭ እንዲሟላ የተዋሕዶ ቁርጠኛ ልጆችን ድጋፍ መጠየቅ አስፈላጊ ሆኗል።

በአሁኑ ሰዓት እንደምታውቁት COVID-19 በተሰኘው መቅሰፍት የተነሳ ቤተ ክርስቲያን መሰባሰብ ባለመቻላችን የቤተ ክርስቲያናችን ገቢም እጅግ ቀንሷል። የደብራችን አስተዳዳሪ አባታችን ያለማቋረጥ በጸሎት እየተማጸኑ ነው። የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አባላትም ከመደበኛ ስራቸው በተጓዳኝ ይሄንን ጉዳይ ለመጨረስ ቀን እና ሌሊት ተግተው እየሰሩ ነው።

እናስተውል! ሁላችንም በሰላም እና በጤና የቆየነው በቸርነቱ ነው እና ለአምላካችን ለክብሩ መገለጫ እንዲሆን፣ ለእኛም መንፈሳዊ በረከት እንድናገኝበት አቅማችን የፈቀደውን ያህል እንድንለግስ በልዑል እግዚአብሔር ስም ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታቀርባለች።

ለግዢ የሚሆነውን ገንዘብ የሚያበድረን ባንክ በነገረን መሠረት አሁን ማሟላት የሚገባን ዝቅተኛው መጠን 150,000 ዶላር ነው እባካችሁ ተባብረን ይቺን እንሙላ።

“እንደ ልቤ የሆነ ሰው ፈቃዴንም ሁሉ የሚያደርግ የእሴይን ልጅ ዳዊትን አገኘሁ።” (ሐዋ ፲፫፡፳፪) ተብሎ በአምላካችን የተመሰከረለት ልበ አምላክ ዳዊት የአምላኩን ቤት ለመስራት እጅግ ተመኝቶ ነበር። ቢሆንም እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ እድሉ የተሰጠው ለልጁ ለሰሎሞን ነው። እኛም የሰሎሞን እድል ተሰጥቶናል።

የዳዊትን ጸሎት እና ምኞት እናስታውስ (መዝ ፻፴፩፡፩-፭)

፩ አቤቱ፥ ዳዊትን ገርነቱንም ሁሉ አስብ፤
፪ ለእግዚአብሔር እንደ ማለ፥ ለያዕቆብም አምላክ እንደ ተሳለ።
፫ በእውነት ወደ ቤቴ ድንኳን አልገባም፥ ወደ ምንጣፌም አልጋ አልወጣም፥
፬ ለዓይኖቼም መኝታ ለሽፋሽፍቶቼም እንቅልፍ፥ ለጕንጮቼም ዕረፍትን አልሰጥም፥
፭ ለእግዚአብሔር ስፍራ፥ ለያዕቆብ አምላክ ማደሪያ እስካገኝ ድረስ ብሎ።

በቅዱስ ዳዊት መንፈሳዊ ቅንዓት ተነሳስተን እንበርታ ህንፃ ቤተ ክርስቲያናችንን በፍጥነት እንግዛ!
 
በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በአባታችን ጸሎት እና ተማጽኖ፣ በምዕመናን ጸሎት እና የገንዘብ ድጋፍ ይህን ህንፃ ቤተ ክርስቲያን በፍጥነት እንግዛ። ለቅዱስ አማኑኤል ወሩፋኤል ታቦት ማረፊያ፣ ለምዕመናንንም ባሰኛቸው ሰዓት መጥተው የሚጽናኑበት እና የሚጸልዩበት መማጸኛ ቦታ ይኑረን።

ህንፃው የቤተ ክርስቲያን ነው፣ ህንፃው የምዕመናን ነው፤ የሚገዛውም በቤተ ክርስቲያን ስም ነው ስለዚህ ደስ ይበለን በደስታም እንስጥ ከአምላካችን ብዙ ተቀብለናልና።

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን

 

ደብረ መንክራት ቅዱስ አማኑኤል ወሩፋኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን

 
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++

In the name of The Father and of The Son and of The Holy Spirit, One God Amen

 

Beloved children of God,

Holy and merciful God, whose bountifulness knows no bounds, has protected us and by God's grace we have been able to see today.

Today is a special day! Almighty God who has kept each one of us in warm and protected houses while He has not found permanent place to establish his church and that is going to come to an end.

                                                                    Praise and glory be to God!

Almighty God creator of all the visible and invisible, Lord Emmanuel who was born in a stable, was exiled with His Holy Mother as a child, was crucified for our sins, gave us His divine flesh and blood for our eternal life; He who gave us all and through Him all things became possible is awaiting the response of His children to partake in the blessings of God by participating in the purchase of a church building. We are chosen for this historic task.

We are indeed lucky to be chosen for this monumental task!

"and build the house; and I will take pleasure in it, and I will be glorified, saith the LORD." Haggai 1:8

We are in the process of securing a loan and facilitating a down payment on a church building we are planning to purchase by the grace of God. The bank we are working with to secure the loan from has set some preconditions for us to maintain a specified cash flow balance. As a church that relies on the generous donations of its congregation we have to turn to the children of God and request the faithful to generously donate whatever they can as soon as possible.

Because the COVID-19 restrictions we have not been able to assemble in church and as a result, donations to our church have been at a very low point for the past several months. The Head of our church, our Father and members of the Parish Council are working hard day and night to successfully finalize the purchase of this church building as soon as possible.

Let's remind ourselves that we are where we are today by the grace of God and although what we mere mortals give is not sufficient to the glory of God; we need to do what we can and partake of the blessings of Almighty God.

Our bank has advised us to maintain a minimum balance of $150,000, please let's come together and meet this minimum requirement!

The bible tells us King David who was favored by God while he was still a shepherd boy, and about who God testified "I have found David the son of Jesse, a man after mine own heart, which shall fulfil all my will." (Acts 13:22). Although David had a strong desire to build the Temple of God, he was not permitted to do so. The chance was given to his son Solomon. We are chosen like Solomon!

Let's remind ourselves the prayer of David (Ps 132:1-5)

1 Lord, remember David, and all his afflictions:
2 How he sware unto the Lord, and vowed unto the mighty God of Jacob;
3 Surely I will not come into the tabernacle of my house, nor go up into my bed;
4 I will not give sleep to mine eyes, or slumber to mine eyelids,
5 Until I find out a place for the Lord, an habitation for the mighty God of Jacob.

Let's rise up in the spirit of David and purchase our church building!!!

By the grace of God, the prayer and beseeching of our Father the Head of our church, the prayer and support of the faithful children of God let's purchase our church building to have a lasting place for the Ark of The Covenant and a place of prayers and refuge for the faithful.

The building is to be purchased in the name of our church, for the use of our church and for the benefit of the faithful children of God. Let's rejoice and give with joy for we have received the bounties of God

 
May the peace of God be upon us all

Debre Menkirat Kidus Amanuel & Rufael Ethiopian Orthodox Tewahdo Church
Donate

Donations 

  • Anonymous
    • $60 
    • 3 yrs
  • Anonymous
    • $60 
    • 3 yrs
  • Anonymous
    • $60 
    • 3 yrs
  • Anonymous
    • $144 
    • 3 yrs
  • Anonymous
    • $72 
    • 3 yrs
Donate

Organizer

Tezeta Tegegne
Organizer
Alexandria, VA
Debre Menkirat Kidus Amanuel and Rufael Ethiopian Orthodox Tewahedo
 
Registered nonprofit
Donations are typically 100% tax deductible in the US.

Your easy, powerful, and trusted home for help

  • Easy

    Donate quickly and easily.

  • Powerful

    Send help right to the people and causes you care about.

  • Trusted

    Your donation is protected by the  GoFundMe Giving Guarantee.