Main fundraiser photo

በእሳት አደጋ ንብረታቸው ለወደመባቸው እገዛ እናድርግ!

Donation protected
ሰሞኑን በጎጃም ግንደወይን በምትባል ከተማ ላይ ያልታሰበ የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ሰዎች ጥረው ግረው ያፈሩት ሀብት በጥቂት ደቂቃ ውስጥ ወድሞባቸዋል:: በእዚህ የእሳት ቃጠሎ የተለያዩ የንግድ ሱቆች የወደሙ ሲሆን ከ30 ሚልየን ብር በላይ ጉዳት እንደደረሰ ተገልጿል:: ይህን ያህል ገንዘብ መልሶ ማግኘትና ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች መልሶ ማቋቋም ከወረዳዋ ህዝብ አንፃር ግዜ የሚወስድ እንደሆነ ይታወቃል::

ስለዚህም እኔ ሄኖክ አበበ ከአሁን በፊት የGofundme አካውንት ከፍቼ እርዳታ ሰብስቤ ባላውቅም አቅሜ በፈቀደው መንገድ ግን ለተለያዩ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች በተለያየ ግዜ እርዳታ ሳደርግ ነበር:: ዛሬ ግን የትውልድ መንደሬ ላይ የደረሰው ጉዳይ ስላሳዘነኝና ጉዳቱ የደረሰባቸው ሰዎች ብዙ ተስፋ ያላቸው በመሆኑና ብዙዎቹ ደግሞ ያላቸው ጠቅላላ ሀብት በመውደሙ እንደገና ለመቋቋም ከባድ ስለሚሆንባቸው ይሄንን በማሰብ ይህን የእርዳታ ማሰባሰቢያ ከፍቻለሁ::

የምትሰጡት የእርዳታ ገንዘብ በግልፅነት ለተጎጂዎች እንዲደርስ እንደማደርግና ለዚህም ማረጋገጫ እዚሁ ማህበራዊ ሚድያ ላይ በግልፅ እንደምለጥፍና እንደማሳውቅ ቃል እገባለሁ:: ለወንድሞቻችን እጃችንን እንዘርጋላቸው::



Organizer

Henok Abebe
Organizer
Hyattsville, MD

Your easy, powerful, and trusted home for help

  • Easy

    Donate quickly and easily.

  • Powerful

    Send help right to the people and causes you care about.

  • Trusted

    Your donation is protected by the  GoFundMe Giving Guarantee.