- S
- Y
- Z
ሰሎሞን ብርሀኔ ስብሀቱ በሜይ 17 ምሽት 8:30 ላይ በዳላስ አክስስ ሮድ ልጆቹን ለማሳደግ ቤተሰቡን ለማገዝ ራይድ በመስራት ላይ እያለ ከዴር ጋር በደረሰ ግጭት በድንገትና በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወቱ አልፏል:: የሰሎሞንን ቀብር ለማስፈፀም እንዲያግዘን የማህበረሰቡን ድጋፍ ለመጠየቅ ተገደናል:: ይህን ጎ ፈንድሚ በባለቤቱ ወ/ሮ ራኬብ ገብረማርያም ወንድም አቶ ቴውድሮስ ገብረማርያም የተከፈተ ነው:: አቶ ሰሎሞን ባለትዳርና የሁለት ታዳጊ ወንድ ልጆች አባት ሲሆን በሜሪላንድ ሲልቨር ስፕሪንግ ነዋሪ ነበር:: ስለእርዳታችሁ አስቀድመን በእግዚአብሔርና በቤተሰቡ ስም እናመሰግናለን::

