Main fundraiser photo

የአቅምዎን በመለገስ አንድ ልጅ ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄድ ያድርጉ!

Tax deductible
"ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፤ እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል።" መዝ 40(41)፥1


በአሜሪካን ሀገር በቨርጂኒያ ግዛት የተቋቋመው የቅዱስ ዮሐንስ በጎ አድራጎት ማኅበራችን በሀገራችን ኢትዮጵያ በብዙ የኑሮ ችግር ውስጥ ወድቀው የሚገኙ ወገኖቻችንን አቅም በፈቀደ መጠን ለመርዳት የተቋቋመ የበጎ አድራጎት ማኅበር ነው !

በዚህም መሠረት ማኅበሩ :-
  • 1ኛ- ወላጆቻቸውን በሞት ያጡና አሳዳጊ የሌላቸውን 24 (ሃያ አራት) ህጻናት፣
  • 2ኛ- በHIV AIDS ( ኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ) ወላጆቻቸውን ያጡ እና እነርሱም ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ 10 አሥር ህጻናት በድምሩ 34 (ሠላሳ አራት) ሕጻናትን የዕለት ምግባቸውን የዓመት ልብሳቸውን በመግዛትና ሙሉ ወጪአቸውን በመሸፈን በቋሚነት ያሳድጋል ::

በተጨማሪም 80 (ሰማኒያ) ለሚሆኑ አረጋውያን እና የአዕምሮ ሕሙማን መኖሪያ ቤት በመገንባት የውሃ ጉድጓድ በማስቆፈር የዓመት ቀለብ በመግዛት ማኅበሩ ለወገኖቹ አጋርነቱን በመግለጽ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ግዴታውን እየተወጣ ይገኛል ::

የበጎ አድራጎት ማኅበራችን በ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ደግሞ አቅም በፈቀደ መልኩ የተረጂዎችን ቁጥር በመጨመር ከ50 -100 ለሚሆኑ ሕጻናት ልብስ ፣ ጫማ ፣ የትምህርት ቁሳቁስ በመግዛትና ተጨማሪ ድጋፍ በመስጠት ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄዱ ለማድረግ አቅዶ እየሠራ በመሆኑ እርስዎን የወገኖችዎን ችግር በመገንዘብና አቅምዎ የፈቀደውን በማድረግ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ግዴታዎን እንዲወጡ በድሆች ወገኖቻችን ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን !!

"መልካም ማድረግን ለሌሎችም ማካፈልን አትርሱ፤" ዕብ 13፥ 16






Donate

Donations 

    Donate

    Organizer

    Tilahun Abebe
    Organizer
    Lorton, VA
    Kidus Yohannes Charity Group
    Beneficiary

    Your easy, powerful, and trusted home for help

    • Easy

      Donate quickly and easily

    • Powerful

      Send help right to the people and causes you care about

    • Trusted

      Our Trust & Safety team works around the clock to keep our community safe