Main fundraiser photo

እድለኛ ትውልድ የአምላኩን ቤት ይሰራል

Tax deductible
“በእርሱም እናንተ ደግሞ ለእግዚአብሔር መኖሪያ ለመሆን በመንፈስ አብራችሁ ትሠራላችሁ” ኤፌ2:22

በሰሜን አሜሪካ በመካከለኛው የካልፎርንያ ግዛት ሳን ሚግየል ከተማ፤ ሞንተረይ ካውንቲ የተቋቋመው እና አዲስ የተገዛው የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የአንድነት ገዳምን መንፈሳዊና ማሕበራዊ አገልግሎት ለማስፋፋት በቋሚነት ሊሠሩ ከታቀዱ ሥራዎች መካከል ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ዋና ሥራ አንዱ በዚህ አገር ተወልደው በማደግ ላይ ለሚገኙ ልጆቻችን እና በልዩ ልዩ ችግሮች ለሚሰቃዩ እና እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያት ወገኖቻችን አስቸኳይና የተሟላ መንፈሳዊ አግልግሎት መስጠት የሚቻልበትን ቅድመ ሁኔታዎች በማዘጋጀት በተግባር ላይ ማዋል የኆኅተ ሰማይ ገዳም ዋና አላማና ራእይ ነው።

በአሁኑ ሰዓት የገዳሙን ቦታ እና አስፈላጊ የግዢ ሰነዶች ተረክበን ገዳሙን ለመንፈሳዊ አገልግሎት በማዘጋጀት ላይ የምንገኝ ሲሆን የፊታችን ሚያዝያ 13 እና 14 2015 ዓ.ም ብፁዓን አባቶች፤ ካህናት፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ዘማሪያን፤ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲሁም የክብር እንግዶች ከተለያዩ የአለማችን ክፍሎች በሚገኙበት ቅዳሴ ቤቱ ይከበራል። እርስዎም በዚህ ታላቅ እና ታሪካዊ በዓል ላይ እንዲገኙልን የአክብሮት ጥሪያችንን እያቀረብን ከዚህ በፊት ለገዳሙ ቦታ ግዢ ላደረጋችሁት ድጋፍና አስተዋፀኦ በእግዚአብሔር ስም እያመሰገንን በቀጣይም ገዳሙ የተገዛበትን ቀሪ የብድር ገንዘብ ለመክፈል እንዲሁም የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት ይቻል ዘንድ በድጋሚ የእርዳታ እጅዎን እንዲዘረጉ በቅዱስ ዮሐንስ እና በቅድስት አርሴማ ስም ጥሪያችችን እናቀርባለን።

ኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የአንድነት ገዳም
Donate

Donations 

    Donate

    Organizer

    Donkey Tube
    Organizer
    San Miguel, CA
    Gateway to Heaven Saint John the Baptist and Saint Arsema Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery
    Beneficiary

    Your easy, powerful, and trusted home for help

    • Easy

      Donate quickly and easily

    • Powerful

      Send help right to the people and causes you care about

    • Trusted

      Our Trust & Safety team works around the clock to keep our community safe