- D
- S
በኢትዮጵያ ሙሉወንጌል በምስራቅ ክልል የሐረር ሸንኮር አጥቢያ ቤተክርስቲያን ከ25 ዓመታት በላይ ስትገለገልበት የነበረው በመጠለያ መልክ የተሰራው የአምልኮ ስፍራ በማርጀቱ በበጋው ጸሀይና በክረምት ዝናብ አገልግሎት ለማካሄድ ከማይመችበት ደረጃ ላይ በመድረሱ እና አሁን እየመጣ ያለውን ትውልድ ታሳቢ ያደረገ ደረጃውን የጠበቀና 94% የሚሆነውንና በወንጌል ያልተደረሰውን የምስራቁን የአገሪቱ ክፍል ለመድረስ የአምልኮ ስፍራና ሚሽነሪዎችን ማሰልጠኛ ስፍራ ለመገንባት መጠነ ሰፊ ስራ ጀምራለች፡፡ ይህንንም ለማከናወን በአገሪቱና በተለያዩ የዓለም ክፍል ያላችሁ ቅዱሳን በግልም ሆነ በተቋም ደረጃ አብራችሁን እንድትቆሙ፤የስራውም ተካፋይ እንድትሆኑ ጥሪአችንን እያቀረብን ከዚሁ ስራ ጋር በተያያ ከዚህ በታች ስማቸው የተጠቀሱት አገልጋዮች በባህር ማዶ እንዲያስተባብሩ የወከልናቸው መሆኑን እየገለጽን አስፈላጊ በሆኑ ነገሮች ሁሉ ድጋፍና ትብብር እንድታደርጉላቸው በጌታ ፍቅር ስንጠይቅ ለሚደረግልን ማንኛውም ድጋፍና ትብብር በቅድሚያ በጌታችንና በአምላካችን ስም እናመሰግናለን፡፡





