Help Jigjiga EOTC Churches &Victims

Foto de la recaudación de fondos Help Jigjiga EOTC Churches &Victims, 1 de 2Foto de la recaudación de fondos Help Jigjiga EOTC Churches &Victims, 1 de 2

  • Y
  • A
  • E
202 donantes
Imagen principal de la recaudación de fondos
0% complete

Se recaudaron $25,168 de $50 mil.

Help Jigjiga EOTC Churches &Victims

Help Jigjiga EOTC Churches &Victims

0% complete

Se recaudaron $25,168 de $50 mil.

202 donaciones
Recently, there has been a violent attack in the Ethio-Somali region targeting Christians. As a result, several people have been killed, more than ten Churches have been destroyed, and several properties have been damaged. We are raising fund to support the victims and rebuild the churches. Please help us with this critical mission in restoring a society in the Ethio-Somali region. May God bless you!

በኢትዮ ሶማሌ ሀገረ ስብከት በተፈጸመው ኢ- ሰብአዊ ድርጊት ለተቃጠሉት አብያተ ክርስቲያናት፣ ለተጐዱት ካህናትና ምእመናን የርዳታና መልሶ ማቋቋም አስተባባሪ ኮሚቴ በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ሰብሳቢነት በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ደረጃ መቋቋሙ ይታወሳል፡: በተከሰተው ግርግርና ግጭት አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፤ ካህናትና ምእመናን ተገድልዋል፤ ንዋየ ቅድሳት ተዘርፈዋል፤ የአብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮችና ምእመናን ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል፡፡

በደረሰው ጉዳት 10 ያህል አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት፣ የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት፣ መንበረ ጵጵስናው፣ የአብነት ት/ቤት ጉባኤ ቤቶች፣ የአጥቢያ ገቢ ማስገኛ ሕንጻዎች እና ሌሎች ንብረቶች ተቃጥለዋል፤ በርካታዎችም ተዘርፈዋል፡፡ እንዲሁም 8 ካህናት ተገድለዋል፡፡ በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ምእመናንና አገልጋዮች ከአጥቢያቸውና ከመኖሪያ ይዞታቸው ተፈናቅለው ለስደት ተዳርገዋል፡፡ አብያተ ክርስቲያናቱን ወደ ነበሩበት ይዞታ መመለስ ይቻል ዘንድ፤ መኖሪያ በታቸውና ንብረታቸው የወደመባቸው ወገኖቻችንን ለዘለቄታው ለማቋቋም፤ እንዲሁም የቤተክርስቲያን አገልጋዮችን ካጋጠማቸው የከፋ አደጋ ለመታደግ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በጠቅላይ ቤተ ክህነት ከተዋቀረው አስተባባሪ ኮሚቴ ጎን እንዲቆም ጥሪ ቀርቧል፡፡ ከደረሰው ጉዳት አንጻር አብያተ ክርስቲያናቱን መልሶ ለማቋቋም ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ በመሆኑና ከኢትዮጵያ ውጪ የሚኖሩ ወገኖችን በድጋፉ ላይ ለማካተት ይቻል ዘንድ ይህ የGoFundMe ገንዘብ ማሰባሰቢያ መንገድ በብጹዕ አባታችን አቡነ ፋኑኤል የዋሺንግተን ዲሲና ካሊፎርኒያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መልካም ፈቃድ ተከፍቶ ወደ ተግባር ተገብቷል፡፡

ይህንን የገቢ ማሰባሰብ ሂደት በሰሜን አሜሪካ በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ስር የሚገኙ መንፈሳውያን ማኀበራት በሰሜን አሜሪካ የካህናት ማኀበር፣ በሰሜን አሜሪካ አኀጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ፣ በማኀበረ ቅዱሳን አሜሪካ ማዕከልና በሰሜን አሜሪካ አኀጉረ ስብከት የማኀበረ በዓለወልድ በመቀናጀት የሚያስተባብሩት ሲሆን የሚሰበሰበው ገንዘብ ተሰብስቦ እንዳለቀ ለዚህ አገልግሎት እንዲውል በኢትዮጵያ በተከፈተው የባንክ ሂሳብ የሚያስገቡ ይሆናል:: በመሆኑም ሁሉም ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊ አብያተ ክርስቲያናቱን ወደ ነበሩበት ይዞታ መመለስ ይቻል ዘንድ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደረግ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡


Organizador y beneficiario

Daniel Alemayehu
Organizador
Silver Spring, MD
Mahibere Kidusan
Beneficiario

Un sitio fácil, eficaz y de confianza donde encontrar ayuda

  • Fácil

    Dona de forma rápida y sencilla

  • Eficaz

    Envía ayuda a la gente y las causas que te importan

  • Confiable

    Tus donaciones están protegidas por la Garantía de donaciones de GoFundMe