Main fundraiser photo

Save AbetirW & Help Displaced Amara

Donation protected

      አበጥር ወርቁ የ14 ዓመት ታዳጊ ነው። እስከ ቅርብ ጋዜ እንደማንኛውም ታዳጊ ብሩህ ተስፋ ነበረው። አበጥር ተወልዶ ባደገበት መተከል (የአሁኑ "ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል") በጉሙዝ ብሄረሰብ ተወላጆች አማራ ስለሆነ ብቻ ለህሊና በሚዘገንን መልኩ ብልቱ ተሰልቦ፣ አይኑ ተጎልጉሎ፣ ፊቱና አካሉ በስለት ተተልትሎ በሞትና በህይዎት መካከል ሆኖ ተስፋው እስከ ወዲያኛው እንዳይጨልም እየታገለ ይገኛል።

     የዚህ ታዳጊ ዘግናኝ ጉዳት በበርካታ አማራ ወገኖቻችን ላይ የደረሰውንና እየደረሰ ያለውን ግፍ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። በአሁኑ ወቅት በርካታ የአማራ ተወላጆች ያለ ምንም ምክንያት ተወልደው ካደጉበት ቀየ "መጤ" ተብለው ንብረታቸውን እየተዘረፉ እየተሰደዱ ሲሆን  እሚደርስላቸው ወገን፣ አቤት እሚልላቸው አካል ይፈልጋሉ።

     አበጥር በአሁኑ ሰዓት በባህዳር ህክምና እየተደረገለት ሲገኝ፣ ከተለያዪ “ክልሎች” “መጤ” ተብለው የተሰደዱ የአማራ ተወላጆች ደግሞ ገሚሶቹ በቤተ ክርስቲያን ገሚሶቹ ደግሞ መጠጊያ አጥተው ጎዳና ላይ ወድቀዋል።

     ይህ ግፍ እንዲቆም አማራና የአማራ ወዳጅ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲጮሁላቸው፣ በፀሎታቸው እንዲያስቧቸው፣ በተቻላቸው አቅም ሁሉ ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው አምባ የአማራ ባለሞያዎች ማህበር አበክሮ ይጠይቃል።

    አምባ የሚሰበሰበውን ገንዘብ አበጥርንና ቤተሰቦቹን ለመርዳት እና በግፍ "መጤ" ተብለው ከትውልድ ቦታቸው የተፈናቀሉ አማሮችን ለማቋቋሚያ ያውላል።


እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!


አምባ የአማራ ባለሞያዎች ማህበር

Organizer

Muluneh Abebe Yimer
Organizer
Leawood, KS

Inspired to help? Start a fundraiser for someone you know

Help someone you know by raising funds and getting their support started.

Your easy, powerful, and trusted home for help

  • Easy

    Donate quickly and easily.

  • Powerful

    Send help right to the people and causes you care about.

  • Trusted

    Your donation is protected by the  GoFundMe Giving Guarantee.