ኢትዮጵያዊያን ሆይ! ኑ የእግዚአብሔርን ቤት እንስራ!
Donation protected
 በፍራንክፈርት ከተማ እጅግ ግዙፍ ቤተ ክርስቲያንና ማእከል የሚሆነው የገዛነው ሕንጻ በፊትለፊት ሲታይ ይህንን ይመስላል፡፡
“ኑ ቤቴን ሥሩ እኔም በርሱ ደስ ይለኛል ይላል እግዚአብሔር“ ት.ሐጌ ፩፣፰
ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር እንዲሉ በመድኃኔዓለም ቸርነትና መልካም ፈቃድ፣ በካህናትና ምእመናን ትብብርና ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከረጅም ዓመታት ያላሰለስ ጥረት በኋላ እነሆ በጀርመን ሀገር በፍራንክፈርት ከተማ እጅግ ግዙፍ ቤተ ክርስቲያንና ማእከል የሚሆን ሕንጻ መግዛታችንን በቅድሚያ ለመላው ኢትዮጵያውያን እናበስራለን፡፡
ይህ ቤተ ክርስቲያን አምልኮት የምንፈጽምበት ቅዱስ ቦታ ከመሆኑም በተጨማሪ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ደስታውንም ሆነ ሀዘኑን በጋራ የሚወጣበት፣ ሕጻናት ሃይማኖታቸውን፣ባህላችውንና ቋንቋቸውን የሚማሩበት በአጠቃላይ በውጭ ሀገር ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ቋሚ አድራሻና የሚያኮራ የታሪክ ቅርስ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡
ይህን ቤተ ክርስቲያን ለመግዛት ከነበረው ከፍተኛ ውጣ ውረድ ባሻገር ለብዙ ዘመናት ምእመናን ያዋጡትን ገንዘብ ባንኩ ምንም ሳያስቀር ከብድር ውላችን ጋር ስላሰበው በአሁኑ ወቅት ቋታችን ባዶ መሆኑን ለመግለጽ ተገደናል፡፡ ስለዚህ ቤተ ክርስቲያኑ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ ውስጣዊ ይዞታውን ማለትም መንበሩን፣ ቤተ መቅደሱን፣ ምንጣፉን፣ የድምጽ ማጉሊያውን፣ ወንበሮቹን፣ ኤሌክትሪኩን፣ ቀለሙንና አጠቃላይ እድሳቱን ወዘተ ለማሟላትና ወርሃዊ ዕዳውን ለመክፈል በርካታ ገንዘብ አስፈላጊ መሆኑ አይዘነጋም፡፡ በዚህም መሠረት ይህ ቤተ ክርስቲያን ለሁሉም ኢትዮጵያዊ አድራሻ፣ ቅርስና ማእከል በመሆኑ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሚችለውን ዕርዳታ እንዲለግስና የታሪክ አሻራውን እንዲያኖር ቤተ ክርስቲያን በመድኃኔዓለም ስም ጥሪዋን ታቀርባለች፡፡
“ኑ ቤቴን ሥሩ እኔም በርሱ ደስ ይለኛል ይላል እግዚአብሔር“ ት.ሐጌ ፩፣፰
ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር እንዲሉ በመድኃኔዓለም ቸርነትና መልካም ፈቃድ፣ በካህናትና ምእመናን ትብብርና ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከረጅም ዓመታት ያላሰለስ ጥረት በኋላ እነሆ በጀርመን ሀገር በፍራንክፈርት ከተማ እጅግ ግዙፍ ቤተ ክርስቲያንና ማእከል የሚሆን ሕንጻ መግዛታችንን በቅድሚያ ለመላው ኢትዮጵያውያን እናበስራለን፡፡
ይህ ቤተ ክርስቲያን አምልኮት የምንፈጽምበት ቅዱስ ቦታ ከመሆኑም በተጨማሪ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ደስታውንም ሆነ ሀዘኑን በጋራ የሚወጣበት፣ ሕጻናት ሃይማኖታቸውን፣ባህላችውንና ቋንቋቸውን የሚማሩበት በአጠቃላይ በውጭ ሀገር ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ቋሚ አድራሻና የሚያኮራ የታሪክ ቅርስ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡
ይህን ቤተ ክርስቲያን ለመግዛት ከነበረው ከፍተኛ ውጣ ውረድ ባሻገር ለብዙ ዘመናት ምእመናን ያዋጡትን ገንዘብ ባንኩ ምንም ሳያስቀር ከብድር ውላችን ጋር ስላሰበው በአሁኑ ወቅት ቋታችን ባዶ መሆኑን ለመግለጽ ተገደናል፡፡ ስለዚህ ቤተ ክርስቲያኑ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ ውስጣዊ ይዞታውን ማለትም መንበሩን፣ ቤተ መቅደሱን፣ ምንጣፉን፣ የድምጽ ማጉሊያውን፣ ወንበሮቹን፣ ኤሌክትሪኩን፣ ቀለሙንና አጠቃላይ እድሳቱን ወዘተ ለማሟላትና ወርሃዊ ዕዳውን ለመክፈል በርካታ ገንዘብ አስፈላጊ መሆኑ አይዘነጋም፡፡ በዚህም መሠረት ይህ ቤተ ክርስቲያን ለሁሉም ኢትዮጵያዊ አድራሻ፣ ቅርስና ማእከል በመሆኑ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሚችለውን ዕርዳታ እንዲለግስና የታሪክ አሻራውን እንዲያኖር ቤተ ክርስቲያን በመድኃኔዓለም ስም ጥሪዋን ታቀርባለች፡፡
Organizer
Sami Ze Nega
Organizer
Frankfurt
Inspired to help? Start a fundraiser for someone you know