Main fundraiser photo

በእንተ ስማ ለማርያም ለእኔ ተማሪ!

Donation protected
Hi, my name is Filimon and I'm fundraising for students who live in Ethiopia and need help, these students are the ones who chose to leave everything behind to serve God with their best abilities, but they need our support to build a school, buy supplies and other necessary things to help them.
read this to understand who the students are and what are their goals.

በእንተ ስማ ለማርያም ለእኔ ተማሪ!

የእውነተኛ ደስታ ምንጭ እግዚአብሔር ነው። እውነተኛ ፀሐየ ጽድቅ ከድንግልማርያም እቅፍ ታይቷል የእውነተኛ ሰላም መገኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተክርስቲያን ነች። የነፍስ ምግቧ ከየኔታ ይደገሳል። የኔታ ወንበር ተክለው ትውልዱን በቃለ እግዚአብሔር በባህል በእሴት እየቀረጹ የዛሬ ተማሪን ለነገ ካህን አድርገው ለነፍሳችን ስርየትን ያሰጣሉ። ይህ ወንበር ቢፈርስ የኔታም ከቦታቸው ባይገኙ የነፍስ መብል ጠፍቶ መንጋው ተበትኖ በክፉ ተኩላ በተበላ ነበር። የኔታ የክርስትና ህይወት ፣የበረከት ፍሬ፣ የሀገር ፍቅር ስላላቸው ዘወትር ቃለ እግዚአብሔርን በመናገር የጠመመውን ሲያቀኑ ፣ ቅኔን ሲዘርፉ፣መፅሐፉትን ሲደጉሱ፣ዜና መዋዕላትን ሲደርሱ፣ሌት ተቀን ከማሓሌቱ፣ከሰዐታቱ፣ከጉባኤ ቤቱ ሳይለዮ ደቀ መዝሙር አፍርተዋል። የኔ ተማሪም ቀዬውን ትቶ ደበሎ ለብሶ በእንተ ስማ ለማርያም በማለት በልጅነት እድሜ ሀገር ለሀገር በመዞር ምሥጢርን ከአባቶቹ ሲማር ከምእመናን ደጃፍ እየተዘከረ ንባቡን ሲቀፅል ቅኔውን ሲዘርፍ ምሥጢርን እያየ ያየውን በቅኔው እያመሰጠረ በቃለ እግዚአብሔር ይመሰጣል ይራቀቃል:: በእንተ ስማ ለማርያም ብሎ ደጅ ጠንቶ ስንቅ አገልግሉ ወላዲተ አምላክን አድርጎ በነገ ተስፋ ዛሬን ይታገላል። የቀየው ሰው የእማምላክን ስም ስንቁ አድርጎ በስሟ ተማፅኖ ለመጣው ተማሪ በፍጹም ፍቅር እና ቅርበት "የኔ ተማሪ መጣ.." እያሉ ከቤት የተገኘውን ጥሬም ይሁን ብስል እየለገሱ መጋቢ እና ሞግዚት በመሆን የዛሬን ተማሪ የነገን ካህን ያለመሰልቸት ያስትምራሉ። ዛሬ ላይ ግን አብሮነት መንምኖ ትውልድን ያስተሳሰረው የአብሮነት ሰንሰለት ተበጥሶ ፍቅር ከቤታችን ሆነ ከልባችን በተሰደደበት በእኛ ዘመን ተሜ ቃለ እግዚአብሔርን እንደተራበ ጥበብን እንደናፈቃት ሳያገኛት በምኞት ይቀራል። ማህበር ቁስቋም አንደኛ አላማው ከሆነው መካከል የቅድስት ሥላሴ ቤተ- መቅደስ የሆነውን የሰው ልጅ በዕውቀት በምግባር ማነጽ ነው። ለዕውቀት ቤቷ የየኔታ ደጅ መሆኑን በማመን በጥናት ባለሙያች ጉዳዩን በማስመልከት በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በማስተቸት የመፍትሄ ሃሳብ በመያዝ ለአብነት ተማሪዎች የምግብ ፣ የመጽሀፍት ፣ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ፣ የህክምና አገልግሎት ፣ መኖሪያ እስከ ማንበቢያ ቤተመጽሐፍት ለማቅረብ የቀደመ ቀናኢነታችሁን በማመን ሥራውን ጀምሯል። በእንተ ስማ ለማርያም ለእኔ ተማሪ! የአብነት ትምህርት ቤትን መደገፍ በወጀብ የማይናወፅ በአለት ላይ የተገነባን የዕውቀት መንደር መፍጠር ነው። ሀገሬ ታሪኳ ሳይጠፋ ቤተክርስቲያኔ ዕሴቷ ሳይጓደል ለልጄ የሚል ኢትዮጵያዊ ሁሉ እጁን ይዘርጋ። የባለታሪክ ልጆችነን እና ታሪክ ላይ ጥቂቷን በማድረግ ታሪክ እንስራ ። ከእውቀት ገጽ የጎደለ ትውልድ እያፈራች ያለች ዓለምን የሚያሸንፈው እምነታችንን በእውቀት የሚከተሉ የነገ ትውልዶችን መደገፍ ለነፍስ ለስጋ በረከት ነው። የዚህ ዓለም ትርጉም በመንፈሳዊነት የሚመዘንበት በጥበብ መነጽር ቤተክርስቲያን የምትታይበት የየኔታን መንደር በመደገፍ ከፍ እናድርጋት።

በገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ:-
በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ:-3900
በአቢሲኒያ ባንክ:-6230
በአካል ተግኝቶ ድጋፍ ለመስጠት የካ ፖሊስ መምሪያ እልፍ ጸጋ ህንፃ 4ተኛ ፎቅ ወይም በአቅራቢያዎ በሚገኝ የማዕከሉ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት::

ሐዋ. ሥራ 20:35፤ እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ፦ ‘ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው፡’ እንዳለ፡ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ።”

********************************************

In the name of St. Mother Mary for my Student!

God is the true source of Joy. The true sun of righteousness is seen from Mary’s hands. A true peace is originated from The Orthodox Tewahido Church. The Fathers (Yeneta) has prepared(planted) their chair to pass on their wisdom, teach the generation word of God in culture and value in a Holy conference to make their disciples a priest who can give the people Atonement from their sin. If this holy assembly is dissolved and If this chair were to be destroyed and the Fathers aren’t available at their designated place, The Nourishment of soul would be lost The shepherd will be left with no flok and the floks will be taken by a wolf. Yeneta having the good Christian life, fruits of blessings, patriotism in their heart always speaking the word of God, envy the corrupt, writing books, praising and worshiping God day and night in Hymn, Holy chant, Mahlet, Kidan, Seatat with out separating from their holy assembly has made a lot of disciples. And My student also left his village, his home, red clothes and dressed in mud in early age traveling country to country to learn the secrets of word of God from his Fathers by making the beloved Mary’s name his Nourishment and shelter. He says “In Mary’s name, open the door and serve food.” The people of the village pleads with God to the student who comes with absolute love and closeness, saying "My student has come.." Donating the raw or cooked food from home, they tirelessly educate the student of today, the priest of tomorrow. Today, however, the chain of solidarity that binds generations has been broken and love has withered. One of the main objectives of the Association Kuskuam is to educate the human being who is the temple of the Holy Trinity through knowledge and conduct. Believing that it is Yeneta's door to the house of knowledge, It has started Its work by believing in your previous zeal to provide food, books, hygiene materials, medical services, housing to reading library for students by investigating the matter and criticizing it by scholars. Supporting this school and project is creating a village of knowledge build up on a solid rock. Let every Ethiopian who wants to pass on a church and a country without losing its history and value to the coming generation should extend their helping hands for the sake of our Church and Country. We are sons and daughters of History makers so lets make a history by contributing even in small ways. It is a blessing for the soul and flesh to support the future generations who follow our faith with knowledge that will overcome the world that is producing a generation that lacks knowledge. Let's support the village of Yeneta, where the meaning of this world is measured spiritually, and the church is seen through the lens of wisdom.

To provide financial support:-
At Commercial Bank of Ethiopia:-3900
Bank of Abyssinia:-6230
To provide support in person, visit the 4th floor of Elf Tsaga Building around megenaya shola yeka Police Department or the nearest branch office of the center.

“I have shown you in every way, by laboring like this, that you must support the weak. And remember the words of the Lord Jesus, that He said, ‘It is more blessed to give than to receive.’ ” Acts 20:35
Donate

Donations 

  • Anonymous
    • $100 
    • 25 d
  • Anonymous
    • $20 
    • 2 mos
  • Anonymous
    • $50 
    • 2 mos
  • Anonymous
    • $20 
    • 2 mos
  • Anonymous
    • $20 
    • 2 mos
Donate

Organizer

Filimon Fiseha
Organizer
Houston, TX

Your easy, powerful, and trusted home for help

  • Easy

    Donate quickly and easily.

  • Powerful

    Send help right to the people and causes you care about.

  • Trusted

    Your donation is protected by the  GoFundMe Giving Guarantee.