help seada mohammed formedical exp
Donation protected
ስሞት አታልቅሱ
ደራሲ፣ ጋዜጠኛ፣ጸሐፊ ተውኔት፣ ገጣሚ እንዲሁም ሁለገብ የኪነ-ጥበብ ባለሙያ ሰዓዳ መሐመድ በኩላሊት ሕመም እየተሠቃየች ነው፡፡
በ1990ዎቹ መጀመሪያ በኢትዮጵያ ሬዲዮ የቅዳሜ መዝናኛና ለወጣቶች ፕሮግራም ድራማ በመጻፍና አጫጭር ጽሑፎችን በማቅረብ የጥበብን ደፍ የረገጠችው ሰዓዳ ፣በዕለታዊ አዲስ ፣በሩሕ ፣በአልነጃሺ፣በአልዋህዳ ጋዜጦች በሪፖርተርነት በአዲስ አድማስ፣በእፎይታ ጋዜጣና መጽሔት በርካታ ጽሑፎችን አስነብባናለች፡፡
"እሾሃማ ወርቅ" የተሰኘ ቤሳ ልቦለድ በማስነበብም የደራሲነት ክህሎቷን አስመስክራለች፡ ይህ መጽሐፏ በርካታ ጥናትና ምርምር አድራጊዎችን የሳበ ነበር፡፡ በ"እፍታ" መጽሐፍ ከቁጥር ሁለት ጀምሮ ባሉ ተከታታይ መጽሐፍት ድርሰቶቿን አስነብባለች፡፡ ፖፕሌሽን ሚዲያ ሴንተር ባሳተማቸው መጽሐፍትም የሷ ድርሰቶች ተካተዋል፡፡ ሰዓዳ ብዕረ ብርቱ ደራሲ ነች፡፡ በተለይ በድራማ አጻጻፍ የተካነች ሆና ብቅ ብላለች፡፡ በቴሌቪዥን ና የሬዲዮ ድራማዎች የሷ እጅ ያላረፈባቸው የዘመኑ ድርሰቶች ጥቂት ናቸው ማለት ይበቃል፡፡
ከ191-1996 በኢዶች የተለያዩ ድራማዎችን በመጻፍ ሥራዎቿ በቴሌቪዥን ፣በመድረክ ቀርቧል፡፡ ሰዓዳ ሁለገብ የጥበብ ሰው ነች፡፡ በ"ዘመን" የቴሌቪዥን ድራማና "በቤት ሥራ" ድራማ ላይ ከጸሐፊዎቹ አንዷ ነች፡፡
ወደፊት ብዙ ለመሥራት እየተዘጋጀች ሳለ የኩላሊት ሕመም ሆስፒታል እንድትምላለስ አድርጓታል፡፡ አሁን የዳያሌሲስ ሕክምና እያካሄደች ነው፡፡ ሐኪሞች የኩላሊት ንቅለ ተከላ ሊደረግላት ይገባል ብለዋል፡፡ ሕክምናውን ለማካሄድ ከፍተኛ ገንዘብ ተጠይቃለች፡፡ ገንዘቡን የመሸፈን አቅም ደግሞ የላትም፡፡ ሁላችሁም ጓደኞቼ ከንፈር ከመምጠጥ ታቅባችሁ እህታችንን እንታደጋት ሕይወቷን እናድን ፣የአቅማችንን እናድርግ፡፡
ደራሲ፣ ጋዜጠኛ፣ጸሐፊ ተውኔት፣ ገጣሚ እንዲሁም ሁለገብ የኪነ-ጥበብ ባለሙያ ሰዓዳ መሐመድ በኩላሊት ሕመም እየተሠቃየች ነው፡፡
በ1990ዎቹ መጀመሪያ በኢትዮጵያ ሬዲዮ የቅዳሜ መዝናኛና ለወጣቶች ፕሮግራም ድራማ በመጻፍና አጫጭር ጽሑፎችን በማቅረብ የጥበብን ደፍ የረገጠችው ሰዓዳ ፣በዕለታዊ አዲስ ፣በሩሕ ፣በአልነጃሺ፣በአልዋህዳ ጋዜጦች በሪፖርተርነት በአዲስ አድማስ፣በእፎይታ ጋዜጣና መጽሔት በርካታ ጽሑፎችን አስነብባናለች፡፡
"እሾሃማ ወርቅ" የተሰኘ ቤሳ ልቦለድ በማስነበብም የደራሲነት ክህሎቷን አስመስክራለች፡ ይህ መጽሐፏ በርካታ ጥናትና ምርምር አድራጊዎችን የሳበ ነበር፡፡ በ"እፍታ" መጽሐፍ ከቁጥር ሁለት ጀምሮ ባሉ ተከታታይ መጽሐፍት ድርሰቶቿን አስነብባለች፡፡ ፖፕሌሽን ሚዲያ ሴንተር ባሳተማቸው መጽሐፍትም የሷ ድርሰቶች ተካተዋል፡፡ ሰዓዳ ብዕረ ብርቱ ደራሲ ነች፡፡ በተለይ በድራማ አጻጻፍ የተካነች ሆና ብቅ ብላለች፡፡ በቴሌቪዥን ና የሬዲዮ ድራማዎች የሷ እጅ ያላረፈባቸው የዘመኑ ድርሰቶች ጥቂት ናቸው ማለት ይበቃል፡፡
ከ191-1996 በኢዶች የተለያዩ ድራማዎችን በመጻፍ ሥራዎቿ በቴሌቪዥን ፣በመድረክ ቀርቧል፡፡ ሰዓዳ ሁለገብ የጥበብ ሰው ነች፡፡ በ"ዘመን" የቴሌቪዥን ድራማና "በቤት ሥራ" ድራማ ላይ ከጸሐፊዎቹ አንዷ ነች፡፡
ወደፊት ብዙ ለመሥራት እየተዘጋጀች ሳለ የኩላሊት ሕመም ሆስፒታል እንድትምላለስ አድርጓታል፡፡ አሁን የዳያሌሲስ ሕክምና እያካሄደች ነው፡፡ ሐኪሞች የኩላሊት ንቅለ ተከላ ሊደረግላት ይገባል ብለዋል፡፡ ሕክምናውን ለማካሄድ ከፍተኛ ገንዘብ ተጠይቃለች፡፡ ገንዘቡን የመሸፈን አቅም ደግሞ የላትም፡፡ ሁላችሁም ጓደኞቼ ከንፈር ከመምጠጥ ታቅባችሁ እህታችንን እንታደጋት ሕይወቷን እናድን ፣የአቅማችንን እናድርግ፡፡
Organizer
idris A idris
Organizer
Inspired to help? Start a fundraiser for someone you know