Electric Power for Lake Tana Debremariam Monastery
We are trying to raise funds for the electrification of St. Mary Monastery of Lake Tana. It is an ancient monastery, founded in 12th Century, located in the outskirts of Bahir Dar, Ethiopia. During the Italian invasion it was used as a hiding place for the holy relics of the nearby churches. Hence it has a very historical significance to the people of the area in addition to the spiritual services offered at the church now to the laity.
The electrification project started back in 2007. The project is estimated to cost around $86,000. Part of the fund is expected to be covered by the local people in Ethiopia. We are hopeful that Ethiopians and friends of Ethiopia will lend their hand for this good cause.
May the blessings of Our Lady Holy Virgin Mary be with us!
የጣና ሐይቅ ደብረ ማርያም ገዳም በባህር ዳር ሀገረ ስብከት ከከተማው በቅርብ ርቀት ጣና ሐይቅ ውስጥ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ ገዳሟ በ12ኛው ክ/ዘመን በአፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት ተመስርታ በአፄ ዓምደ ጽዮን ዘመን ተገድማለች፡፡ በቀደምትነቷም የ”ባህርዳር እናት” በመባል ትታወቃለች። በአካባቢው ቤተክርስቲያን ባልተመሰረተበት ወቅት ጀምሮ እስካሁን ድረስ ለአካባቢው ምዕመናን መንፈሳዊ አገልግሎት ከመስጠት ሳታቋርጥ የኖረች ገዳም ናት፡፡ በጣሊያን ወረራ ወቅትም የባህር ዳር ጊዮርጊስ ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ሲቃጠል አባቶች ታቦቱን በታንኳ ወደ ደሴቲቷ አስገብተው ገዳሟ መጠለያ ሆና እንደነበር ታሪክ ያስረዳል።
ገዳሟ ምንም እንኳ ጥንታዊትና ታሪካዊት እንዲሁም ለባህር ዳር ከተማ ቅርብ ብትሆንም እስካሁን ድረስ የኤሌክትሪክ መብራት አገልግሎት ማግኘት አልቻለችም፡፡ ከ2000ዓ.ም ጀምሮ መብራት ለማስገባት እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን በ2013 ዓ.ም. ከመብራት ኃይል በተሰጠ ግምት መሰረት ከ3.6 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንዲደረግ ተጠይቋል። ገንዘቡን የአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ሰበካ ጉባኤው በቀላሉ ሊሸፍኑት የሚችሉት አይደለም፡፡ ስለሆነም የሀገርና የቤተ ክርስቲያን ወዳጆች የአቅማችሁን በመርዳት ስራውን ፍጻሜ እንዲደርስ ትብብራችሁን በወላዲት አምላክ ስም እንጠይቃለን፡፡
ለዚህም ለእርዳታ ማሰባሰቢያ ከቤተክርስቲያኗ የተጻፈውን ህጋዊ ደብዳቤና እርዳታውን እንዲያሰባስብ የተቋቋመውን የኮሚቴ ዝርዝርና ሀላፊነት የያዘ ደብዳቤ ከታች ይመልከቱ፡፡ የቤተ ክርስቲያኗ የባንክና የስልክ ቁጥር በደብዳቤው ላይ ይገኛል።
የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከት አይለየን!