ዳግማዊ ዋልድባ በካሊፎርኒያ ግዛት በሀገረ አሜሪካ
Tax deductible
“በእርሱም እናንተ ደግሞ ለእግዚአብሔር መኖሪያ ለመሆን በመንፈስ አብራችሁ ትሠራላችሁ” ኤፌ2:22
በሰሜን አሜሪካ በመካከለኛው የካልፎርንያ ግዛት ሳን ሚግየል ከተማ፤ ሞንተረይ ካውንቲ የተቋቋመው እና አዲስ የተገዛው የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የአንድነት ገዳምን መንፈሳዊና ማሕበራዊ አገልግሎት ለማስፋፋት በቋሚነት ሊሠሩ ከታቀዱ ሥራዎች መካከል ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ዋና ሥራ አንዱ በዚህ አገር ተወልደው በማደግ ላይ ለሚገኙ ልጆቻችን እና በልዩ ልዩ ችግሮች ለሚሰቃዩ እና እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያት ወገኖቻችን አስቸኳይና የተሟላ መንፈሳዊ አግልግሎት መስጠት የሚቻልበትን ቅድመ ሁኔታዎች በማዘጋጀት በተግባር ላይ ማዋል የኆኅተ ሰማይ ገዳም ዋና አላማና ራእይ ነው።
በአሁኑ ሰዓት የገዳሙን ቦታ እና አስፈላጊ የግዢ ሰነዶች ተረክበን ገዳሙን ለመንፈሳዊ አገልግሎት በማዘጋጀት ላይ የምንገኝ ሲሆን የፊታችን ሚያዝያ 13 እና 14 2015 ዓ.ም ብፁዓን አባቶች፤ ካህናት፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ዘማሪያን፤ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲሁም የክብር እንግዶች ከተለያዩ የአለማችን ክፍሎች በሚገኙበት ቅዳሴ ቤቱ ይከበራል። እርስዎም በዚህ ታላቅ እና ታሪካዊ በዓል ላይ እንዲገኙልን የአክብሮት ጥሪያችንን እያቀረብን ከዚህ በፊት ለገዳሙ ቦታ ግዢ ላደረጋችሁት ድጋፍና አስተዋፀኦ በእግዚአብሔር ስም እያመሰገንን በቀጣይም ገዳሙ የተገዛበትን ቀሪ የብድር ገንዘብ ለመክፈል እንዲሁም የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት ይቻል ዘንድ በድጋሚ የእርዳታ እጅዎን እንዲዘረጉ በቅዱስ ዮሐንስ እና በቅድስት አርሴማ ስም ጥሪያችችን እናቀርባለን።
ኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የአንድነት ገዳም
Fundraising team (9)
Saint JTBM Task Force
Organizer
Creston, CA
SAINT JOHN THE BAPTIST & ST ARSEMA ETHIOPIAN ORTHODOX TEWAHEDO MONASTERY
Registered nonprofit
Donations are typically 100% tax deductible in the US.
Mulate Abate
Team member
Tersit Ceta Benvegnu
Team member
Eskinder Mengesha
Team member
Alebachew Yimer
Team member